ምክር ቤቱ የልምድ ልውውጥ መድረክ አካሄደ።

Share: Facebook | Twitter | Whatsapp | Linkedin Visits: 10


ምክር ቤቱ የልምድ ልውውጥ መድረክ አካሄደ።

ምክር ቤቱ የልምድ ልውውጥ መድረክ አካሄደ። የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጋር የልምድ ልውውጥ መድረክ አካሂዷል። የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት ጽ/ቤት ሀላፊ ክብርት ወ/ሮ ጀዋሪያ ቀሊ ይህ አይነቱ በተቋማት መካከል የሚደረግ የልምድ ልውውጥ ለተቋማት ግንባታ ወሳኝ መሆኑን በመግለጽ ክፍተቶችን ለይቶ እርምት ለመውሰድም አጋዥ መሆኑን ጠቁመዋል ። የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ መነቴ ሙንዲኖ በበኩላቸው የልምድ ልውውጡ መድረኩ በርካታ ተሞክሮዎች የተገኙበት መሆኑን ገልጸው፤ ለተደረገላቸው አቀባበል እና ማብራሪያ አመስግነዋል ። በመድረኩ ከአደረጃጀት ፣የተቋም ክትትልና ቁጥጥር ስራዎችን በሚመለከት፣ የህግ አወጣጥ ሂደት በተመለከተ፣ ከህዝብ ግንኙኝነት ስራዎችን አኳያ እንዲሁም አጠቃላይ የምክር ቤት ጽ/ቤቱ የስራ ክንውኖችን አስመልክቶ ሰፊ ማብራርያ ተሰጥቷል ።



Leave a Comment: